የባሌ ሮቤ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ግንባታ ፕሮጀክት /Bale Robe Rural Transformations Centre Project

የባሌ ሮቤ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ግንባታ ፕሮጀክት /Bale Robe Rural Transformations Centre Project/ በድርጅታችን አለማየሁ ከተማ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ አጥጋቢ በሚባል ሁኔታ በመገንባት ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የሚገኘውን ከፍተኛ የሆነ የእህል አቅርቦት እና የእንስሳት ተዋጽዎ ለማቀነባበር የሚረዳ ሲሆን ለአካባቢው ነዋሪዎችም ከፍተኛ የስራ ዕድልን የሚፈጥር ነው። ድርጅታችንም የፕሮጀክቱን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ በመረዳት ሥራውን በጥራት በመስራት በተቀመጠለት የጊዜ ሠሌዳ አጠናቆ ለመንግስት ለማስረከብ ቀን ከሌሊት በታላቅ ትጋት በመስራት ላይ ይገኛል። ከዚህ በተጨማሪም በአካባቢው የሚገኘውን ማህበረሰብ የኑሮ ሁኔታ በተጨባጭ ለማሻሻል የሚረዱ መልካም ተግባራት ላይ በመሰማራትም ላይ ነው። የዘይበላ አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶት እድሳት እና የ ጤና ተቋም ግንባታ ለዚህ ዓይነተኛ ምሳሌዎች ናቸው።

Related posts

Leave your comment Required fields are marked *

X